Search

Showing posts with label Who is. Show all posts
Showing posts with label Who is. Show all posts

Wednesday, August 7, 2013

Gedion Zelalem

 Zelalem holds German as well as Ethiopian nationality. Zelalem moved with his family from Berlin to the United States in 2006.

The Promising midfielder Gedion Zelalem,who is eligible to play for Ethiopia but has represented Germany at U15 and U16 levels, is regarded within the club as a prodigious talent.

Gedion Zelalem Meets Drogba

Wednesday, April 10, 2013

Author Bealu Girma "found' in Bahir Dar


ደራሲ በአሉ ግርማ በባህርዳር ጣና ሐይቅ ዙሪያ አለም በቃኝ ብሎ ሞንኩሶ እግዚአብሄርን እያገለገለ መሆኑ ታወቀ !!!

 

ዛሬ ማምሻውን ከወደ ባህርዳር አካባቢ የተሰማው ወሬ በርካቶችን እያስገረመ እና እያስደነገጠ ይገኛል፡፡ በርካታ ኢትዮጲያውያን በእጅጉ የሚያደንቁት፣ ነገር ግን በደርግ መንግስት ታፍኖ የደረሰበት ያልታወቀው ደራሲ በአሉ ግርማ በባህርዳር ጣና ሐይቅ ዙሪያ ከሚገኙ ደሴቶች አንዱ በሆነው የዳጋ እስጢፋኖስ ገዳም ውስጥ አለም በቃኝ ብሎ ሞንኩሶ እግዚአብሄርን እያገለገለ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ቀደም ሲል በይስማእከ ወርቁ ደራሲነት የምናውቃቸው ዴርቶጋዳ፣ራማቶሃራ፣ዣንዥድ እና ተልሚድ የተሰኙ ስራወች የደራሲ በአሉ ግርማ መሆናቸው እና
በይስማዕከ ወርቁ አማካኝነት የወጡ መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡ ይሄ ወሬ ከተሰማ በኋላ በርካታ የባህርዳር ነዋሪወች የዳጋ ደሴትን ያጨናነቁ ሲሆን የአዲስአበባና የሌሎች የሃገራችን ክፍል ነዋሪዎችም ነገ በማለዳ ወደ ባህርዳር ጉዞ ለማድረግ ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ መኪና እና የፕሌን ትኬቶች ተሽጠው ያለቁ ሲሆን የኢትዮጲያ አየር መንገድም ነግ እና ከነገ በስቲያ ወደ ሌሎች የሃገራችን ክፍሎች የሚደረጉበረራዎችን ሰርዞ ጉዞ ወደ ባህርዳር ብቻ እንደሚያደርግ ተነግሯል.
Source: addisuwond.wordpress.com


ትኩስ ነገር ይህንን ዜና ይህ ዜና post እስተደረገ ግዜ ማረጋገጥ አልቻዕችም

 

Friday, April 5, 2013

Liya Kebede

There are some who say that beauty is only skin-deep, and that many who appear beautiful outside may not be as good on the inside. But if you meet Liya Kebede, you would definitely prove these people wrong. Her natural, flawless beauty on the outside is matched by her compassionate and loving heart. Let us learn more about this fantastic woman and see what makes her so extraordinary.
Liya Kebede is a world renowned fashion supermodel, designer and women’s advocate who has appeared numerous times in several famous fashion magazines such as Vogue, and has been featured in numerous fashion shows by popular fashion brands such as Victoria’s Secret, Dolce & Gabbana, Louis Vuitton, Tommy Hilfiger, Escada, Emanuel Ungaro, and Yves Saint-Laurent.
Liya is also the first woman of color that represented the Estee Lauder brand, a world famous company that manufactures skin care, make-up, fragrance, and hair care products.
Liya’s natural beauty and talent for modelling has allowed her to become a very successful fashion model to the point that she is currently listed as one of the World’s Top Earning Models by Forbes magazine, making Liya only the second Ethiopian to have been included in the Forbes magazine’s Richest List, the first one being Mohammed Al Amoudi.
Many fashion critics have praised Liya for being such a natural in the modelling industry. Whenever Liya steps up to the ramp and walks during a fashion show, she brings such a surprise to the crowd by making her poses seem very effortless for her. Liya has such a talent for modelling that even James Scully, a talent hunter who is responsible for picking the models who would walk on the top runways, keeps getting amazed by Liya. He said of her during an interview:
“An all-time eternal favorite for me — she's an exotic Grace Kelly. Models work for years to develop the poise, grace, and style that she came to the business already equipped with! It still shocks me that I sometimes have to sell her to a client, but every time she walks in the room, she always proves me right.”
Liya’s spectacular rise to fame and stardom in the fashion world is an inspiring story in itself because during that time, only the Caucasians dominated the runways. There were many times in her earlier career that Liya was turned down simply because she was of a different color, but she never let the critical voices weigh her down. When she developed her goal and desire of becoming a fashion model, Liya never let the obstacles stop her from reaching the goal – it kept her going on and on, being persistent in spite of all the negative situations and voices that tried to discourage her. In an interview made with her, Liya stated:
“If you don't have a dream in life, I don't know what you have. You have to want something beyond your reach; it's exciting when it works out.”
Liya is also a well-known businesswoman, having founded her own company which she named Lemlem. Lemlem, which in her mother tongue means “to bloom”, is Liya’s way of not only preserving and promoting Ethiopian culture, but is also her means of giving jobs to her fellow countrymen by having the clothes made by hand in Ethiopia. Lemlem designs are being sold in many boutique shops around the world today, such as Barney’s, J.Crew and Net-a-Porter.com.
But apart from all the successes that Liya has achieved in her career, what makes her very fascinating is for her to have the time to engage herself in philanthropic work. Liya is an active advocate of maternal welfare, and is a World Health Organization Ambassador for Maternal, New born and Child Health.
Liya has also founded her own charitable organization, the Liya Kebede Foundation, in an effort to reduce the mortality rates of pregnant mothers and newly-born children around the world. In an interview, Liya revealed how she has the desire of helping mothers and children internationally:
“I am driven by the desire to help save the lives of mothers and children worldwide. I was lucky to give birth in New York City, so I didn’t have to worry about whether my child and I would survive. I am grateful to be a maternal health advocate. It’s something that gives me so much back.”
Currently, Liya actively engages in her activities as a philanthropist, entrepreneur, and especially as a model. She also exposes herself more in the show business, but she says that she would still put modelling above a show business career. She states:
“Modeling still excites me. It is a great form of expression for me. I have been lucky enough to work with incredibly talented people. I’ll never forget seeing my first French Vogue cover and spread. Seeing all those images of myself in a magazine like that — it gave me such a thrill! Another exciting moment was my first American Vogue shoot. It was a big group shot, of all top models, by Steven Meisel. I was in awe. And smitten with the profession.”

Friday, March 1, 2013

Netsanet Melesse_ A look at her music career

 A short story of Netsanet Melesse
Netsi one of the best singers who are legend and sings for real. Not for money, not for crowed but for deep Interest for music.
Ere min honehal Semonun ante sew was one of the your  unforgettable music for every Ethiopian listeners. It's a listeners number 1 choice. Netsi's musical legacy speaks for itself that her voice will takes u over.

Saturday, February 23, 2013

በፍርሃትና በጩኸት እንደ እያሪኮ ግንብ የምፈርስ አይደለሁም”


ወ/ሮ ሙሉ ሠለሞን፤ የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት)
በደርግ ዘመን በኢትዮጵያ ኢምፖርት ኤክስፖርትና የችርቻሮ ኮርፖሬሽን ውስጥ ነው ስራ የጀመሩት፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በፀሐፊነት አገልግለዋል በቢዝነስ ቢኤ ዲግሪ፣ በኢንቫይሮመንትና ዴቨሎፕመንት ማስተርስ ያላቸው ወ/ሮ ሙሉ ሰለሞን፤ አሁን ደግሞ በሊደርሺፕና ኢንተርፕሪነርሺፕ ፒኤችዲያቸውን እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ “ራይት ቪዥን” የተባለ ኩባንያ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ የሆኑት ወ/ሮ ሙሉ፤የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት የመጀመርያዋ ሴት ፕሬዚዳንት በመሆን በማገልገል ላይ ናቸው፡፡ የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ናፍቆት ዮሴፍ በንግስተ ሳባ ሆቴል በነበራቸው ቀጠሮ በሥራና ተመክሮ፣ በስኬትና ፈተና፣ በህይወትና ራዕያቸው ዙሪያ ያደረገችው ቃለምልልስ እንደሚከተለው ተጠናቅሯል፡፡
ለኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ፕሬዚዳንትነት ያደረጉት ውድድሩ እንዴት ነበር? 
በመሠረቱ ምክር ቤቱን ቀደም ብዬም አውቀዋለሁ፡፡ ምክንያቱም አዲስ አበባ ቻምበርን በዳይሬክተርነት አገልግያለሁ፡፡ በበጐ ፈቃደኝነት በተለያዩ ማህበራት ውስጥም ሰርቻለሁ፡፡ አሁን ደግሞ የራሴ ስራ ላይ ላተኩር ብዬ ባሰብኩበት ሰዓት ነው ወደዚህ ውድድር የገባሁት፡፡ አዲስ አበባ ቻምበር ዳይሬክተር የሆንኩት በከፍተኛ ድምጽ ተመርጬ ነው፡፡ እንደውም ፕሬዚዳንት እንድሆንም ብዙ ግፊቶች ነበሩ፡፡ ሆኖም በግሌ የምመራቸውና የምሠራቸው በርካታ ነገሮች ስለነበሩ በወቅቱ ጥያቄውን አልተቀበልኩም፡፡
የሆነ ሆኖ እኔ የአዲስ አበባ ቻምበር ዳይሬክተር ሆኜ ከ1997 ምርጫ ጋር ተያይዞ በተከሰተው ቀውስ ከሱቆች መዘጋትና ከመሳሰሉ ነገሮች ጋር በተገናኘ ፈታኝ ወቅት ነበር፡፡ ታዲያ ሱቆችን ከማስከፋት ጀምሮ አጠቃላይ የንግዱ ማህበረሰብ ወደቀድሞው መረጋጋትና የንግድ ሥርዓት እንዲገባ፣ነጋዴው በራሱ ካጠፋ እንዲጠየቅ፣ነገር ግን ድርጅቶቹ ሥራቸውን እንዲቀጥሉ የማድረግ ፈታኝ ወቅት አሳልፈናል፡፡ ያ ወቅት በጣም አስቸጋሪ ነበር፡፡
ለኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ም/ቤት የተወዳደርኩት ያለ አንዳች ተቃውሞ ሲሆን እንድወዳደር ፈርመው ነው የኔን ስም የላኩት፡፡ ነገር ግን እኔ ብዙ የራሴ ሥራ አለኝ፡፡ የአዲስ አበባውን አገልግያለሁ፡፡ ያላገለገሉ ስላሉ እነሱ ይወዳደሩ ብልም ጫናው በዛ፡፡ ምናልባት አንድም ሁለትም አመት አገልግለሽ ብትተይው ይሻላል፣ይሄ ሁሉ ሰው ያለ አንዳች ተጣባባቂ አንቺን አምኖ ሲያወዳድር እንዴት እምቢ ትያለሽ--- የሚል ጫና በረታና ተወዳደርኩኝ፡፡ በዚህ ደግሞ ሌላ ጫና ገጠመኝ፡፡
ምን ዓይነት ጫና?
ምን መሰለሽ? የበፊቱ ፕሬዚዳንት አቶ ኢየሱስ ወርቅ ዛፉ መቀጠል ይፈልጉ ነበር መሠለኝ ከየአቅጣጫው በስልክ ዛቻና ማስፈራሪያው በዛ፡፡ በአካልም መጥተው አርፈሽ ተቀመጪ፣ ቦታውን ስለሚፈልጉት ከውድድሩ ራስሽን አግልይ ያሉኝ ነበሩ፡፡ በስልክም የማላውቃቸው ሰዎች “አርፈሽ ልጆችሽን አሳድጊ” ይሉኝ ነበር፡፡ ማንነታቸውን ግን አይገልፁም፣ እኔ ደግሞ በጩኸትና በፍርሃት እንደ እያሪኮ ግንብ የምፈርስ አይነት ሰው አይደለሁም እና ጉዳዩ የበለጠ እንድፀና አደረገኝ፡፡ ለምሣሌ ሚዲያ ተቋሙንም የጋዜጠኞችንም ሥም መጥቀስ ባልፈልግም ሴት ጋዜጠኞች ማበረታታት ሲገባቸው ያቀርቡልኝ የነበረው ጥያቄ የንቀትና የማስፈራራት አይነት ነበር፡፡
እስቲ ከእርስዎ ጋር የተወዳደሩትን ሰዎች ይንገሩኝ----
ለውድድር የቀረብነው አራት ሰዎች ነን፡፡ አንደኛው ተወዳዳሪ የቀድሞው ፕሬዚዳንት አቶ ኢየሱስ ወርቅ ዛፉ ናቸው፡፡ አባልነታቸው አዲስ አበባ ቢሆንም ከአዲስ አበባ አልተወከሉም፡፡
ህጉም የሚለው ካለሽበት ክልል ተወክለሽ ነው የምትወዳዳሪው፣ካለሽበት ክልል ተወክለሽ ግን የትኛውም ክልል ሊመርጥሽ ይችላል፡፡ አቶ ኢየሱስ ወርቅ የተጠቆሙት ከሌላ ክልል ነበር፣ይህም የምርጫው ቀን ጭቅጭቅ አስነስቶ ነበር፡፡ ሌላው ጌታቸው አየነው ከአማራ ክልል ነበር፣ሶስተኛው የማላውቀው ሰው ነበር - ለውድድሩ አልቀረበም፣ እኔ አራተኛ ነኝ፡፡ ለምክትል ፕሬዚዳንትነትና ለቦርድ አባልነት የሚወዳደሩም ነበሩ፡፡ ለውድድሩ ንግግር ስናደርግ ከአማራ ክልል የመጣው ራሱን አገለለ (ሪዛይን አደረገ)፣ አንደኛው መጀመሪያውኑም አልመጣም፣ ስለዚህ እኔና አቶ ኢየሱስ ወርቅ ብቻ ቀረን፡፡ እዛ ውድድር ላይ ቀድሞ የተሠራ ሥራ እንደነበር ፍንጮች ነበሩ እናም በሻይ ሰዓት “እናንተ በቃ ሴት አትመርጡም አይደል” እያልኩ እቀላልድ ነበር፡፡
ቀደም ብሎ የተሠራው ስራ ምንድን ነው?
እሣቸውን ለመምረጥ ተማምለው የመጡ እንደነበሩ መረጃ አለኝ፣በአንደበታቸውም ይህንኑ የነገሩኝ አሉ፡፡ የሆነ ሆኖ እኔ እዚህ ተወዳድሮ በመመረጥ እንጂ በሌላ ሌላው አላምንም፣ መሆንም የለበትም፣ ስለዚህ ውድድሩ ቀጠለ፡፡ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተጀምሮ 10፡00 ሰዓት ማለቅ የነበረበት እስከ ሌሊቱ ስድስት ሰዓት ማለቅ አልቻለም፡፡ ምክንያቱም ብዙ ጫናና ፍትጊያ ነበር፡፡ ብጥብጥ እንዲፈጠር የሚፈልጉ ሰዎችም ነበሩበት፡፡ የሆነ ሆኖ እርሳቸው ንግግር አድርገው ሲጨርሱ እኔ በተራዬ ንግግር ካደረግኩ በኋላ አብላጫው ሰው ፊቱን ወደኔ አዞረ፡፡
ድምጽ ተቆጥሮ አሸናፊው እስከሚነገር ከአንድ የማላውቃቸው የክልል ንግድ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ጋር ስናወራ “እኛ አንችን አናውቅሽም ስለዚህ የምናውቀውን ለመምረጥ ስምምነት ነበረን፡፡ ነገር ግን ንግግር ስታደርጉ ሁሉም ወዳንቺ ተገለበጠ” አሉኝ፡፡
ሌሎችም እንዲሁ ወንዶችም ሴቶችም ንግግሬን እስኪሰሙ አቋማቸው የእኒህ ሰውዬ አይነት እንደነበር ነግረውኛል፡፡ በዚህ ሁኔታ ነው ያሸነፍኩት፡፡ እኔ 132፣ እሣቸው 62 ድምጽ ነበር ያገኘነው፡፡
ምን አይነት ንግግር ቢያደርጉ ነው መራጮችን መማረክ የቻሉት?
እኔ የተናገርኩት ብዙ ከባድ ንግግር አይደለም፡፡ ምን አልኩ መሰለሽ? “እኔ እንደ ድሮ ፓርላማ - መንገድ አሠራላችኋለሁ፣መብራት አስገባላችኋለሁ አልልም፡፡ ከአዲስ አበባም ልመረጥ ከሌላም ልወከል ለላከኝ ክልል ወይም ቻምበር ሳይሆን ለሁላችሁም የኢትዮጵያ ማህበር አባላት በቀናነት አገለግላለሁ፡፡ ነገር ግን ከዚህ ከተወከለች ለእኛ ትሠራለች ለዚህኛው ወገን በቅርበት ትሠራለች የሚል የተከፋፈለ ሃሳብ ካላችሁ አትምረጡኝ፡፡ ለእውነትና ለሃቅ ፊት ለፊት የምጋፈጥ ስለመሆኔ ታውቃላችሁ” ከዚህ በላይ ብዙ መናገር አላስፈለገኝም ነበር፡፡
የሃላፊነት ቦታው ግን እስካሁን ድረስ ከሽኩቻ እንዳልፀዳ ይነገራል------
በፊት የነበሩ ሰዎች መቀጠል ነበረብን የሚል ቁጭት አለ፣ አሁንም የሷን ስራ እናበላሻለን ይላሉ፣ የኔ ሳይሆን የመንግስትና የህዝብ ስራ ነው የሚሠራው፡፡ ስለዚህ ይሄ ነገራቸው የበለጠ እንድንሰራ ያደርገኛል እንጂ አያሰንፈኝም፡፡
የድሮ ሰው ምቀኛ አታሳጣኝ የሚለው ለምን ይመስልሻል፡፡ ሰው ሲቃወምሽ አንዳንዴ ስህተትሽንም ትመለከቻለሽ፣በጭፍን ጥላቻ የሚያወራብሽም ከሆነ ዘግተሽው ስራሽን ትቀጥያለሽ አለቀ፡፡ በወሬ ጊዜያቸውን ባያባክኑ ግን ደስ ይለኛል፡፡ እኛ በአሉባልታ ጊዜ እንድናባክን ይፈልጋሉ፣እኛ ለወሬ ጊዜ የለንም አለቀ፡፡ ሥራ ላይ ነን፡፡ ለውጥ ላይ ነን፡፡
አሸንፈው ሃላፊነቱን ሲረከቡ በቅድምያ የጠበቅዎት ስራ ምን ነበር? እስካሁንስ ምን አከናወኑ?
ብዙ ሊስተካከሉ የሚገቡ ሥራዎች ሊጠብቁሽ ይችላሉ፡፡ አንድ አገርኛ አባባል ልንገርሽ፡፡ የዱሮ ባሎች የመጀመርያ ሚስት ፈትተው ሌላ ሚስት ሲያገቡ፣ አዲስ የተገባችው ሴት የመጀመሪያዋ የሠራችውን መደብ አፍርሳ ከዛ የባሰ የተበላሸ መደብ ትሠራለች ይባላል፡፡ እሷ ያንን የምታደርገው ከጀመሪያዋ የተሻልኩ ነኝ ለማለት ነው፡፡ እኔ እንደ አዲሷ ሚስት ያለ አመለካከት የለኝም፡፡ አዲስ የተመረጡት የቦርድ አባላትም ጭምር፡፡ እከሌ በነበረበት ጊዜ ይህን አላደረገም ይህን አበላሽቷል ብሎ የማጣጣል ፍላጐትም ሃሳቡም የለንም፡፡ በነበረው አሠራር ጥሩ ነው ያለውን እንቀጥልበታለን፡፡
የተበላሹ ካሉ እያስተካከልን የመሄድ ሃሳብ ነው የነበረን፡፡ በጣም የሚገርምሽ የምርጫው ዕለት እኔ ሳሸንፍ ህዝቡ “ሳዳም ወረደ፤ጋዳፊ ወረደ” እያሉ ሲጨፍሩ ሊቀመንበሩ ማስቆም አልቻሉም ነበር፡፡ እኔ ድምጽ ማጉያውን ተቀብዬ “ከእኔ ጋር መስራት የምትፈልጉ ከሆነ እንዲህ አይነት ንግግር አልፈልግም፡፡ እኔ የሠላም አምባሳደር ነኝ፤ በሠላምና በፍቅር ነው መስራት የምፈልገው፡፡ የሚሠራው ሰው ይሳሳታል ያጠፋል፤ ያም ቢሆን እስከዛሬ ያገለገለ ሰው መመስገን እንጂ መሰደብ የለበትም፤አሁኑኑ ይህን አይነት ስድብና ጭፈራ ካላቆማችሁ ትቼ እሄዳለሁ” ስል ሁሉም በአንድ ጊዜ ፀጥ አሉ፡፡
ይታይሽ “ሳዳም ጋዳፊ ወረደ” የሚሉት እሳቸው ባሉበት ነው፤ የሠራ ሰው በፍፁም መሰደብ የለበትም፡፡ በእለቱ እኔ ምን አልኩኝ፤“ድግስ ደግሰን ጋብዘን ሸልመንና አመስግነን እንሸኛቸዋለን” ይህንንም አድርገናል፤ሚኒስትሮች ባሉበት ራት ጋብዘን፤ ለቦርዶቹ ደረት ላይ የሚደረግ የቻምበሩ አርማ ያለበት ወርቅ ሸልመን ነው የሸኘናቸው፡፡
ሥራውን ሲጀምሩት በጣም ፈታኝ የሆነብዎ ምን ነበር?
በጣም ፈታኝ የምለው ስራ በኢትዮጵያና በአዲስ አበባው ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤቶች መካከል ጠብ ነበር፡፡ ጠላትነታቸው ደግሞ ለ40 ዓመታት ሥር የሰደደ ነው፡፡ እኔ ወደ ኢትዮጵያ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ስመጣ ሁኔታው በጣም የከፋ ነበር፡፡ ብቻ ምናለፋሽ ጥሩ ሁኔታ አልነበረም፡፡ ሰዎች የሁለቱን ቻምበሮች ጉዳይ እንዳትነኪ፤ ዝም ብለሽ ቀጥይ ይሉኝ ነበር፡፡
የጠባቸው መንስኤ ምንድን ነው?
አንዱ የሚያጣላቸው የህንፃው ጉዳይ ነው፡፡ ሌላው የስራ መመሳሰል ነው፡፡ ለምሣሌ አዲስ አበባ ቻምበር ይህን ይሠራል፤የኢትዮጵያ ይህን ይሠራል እየተባባሉ፡፡ ተባብረውና ተቻችለው መስራት ሲችሉ ይበጣበጡ ነበር፡፡ እኔ ለጉዳዩ እልባት ለማግኘት ስሞክር፤ሁለቱን ቻምበሮች ለማስታረቅ እንዳትሞክሪ፤የህንፃውን ጉዳይ እንዳትነኪ እባላለሁ፡፡ እኔ ደግሞ መስራት ካለብኝ ሠላምና የረጋ መንፈስ ባለው ሁኔታ ነው የምሠራው፡፡ ይህን አትንኪ ያንን አታንሺ የሚባለውን ነገር አላመንኩበትም፤እስከመቼ ነው ሳትነኪ የምትኖሪው? ችግርን ቀርበሽና ተጋፍጠሽ እንጂ በመፍራትና በመሸሽ መፍትሔ አታመጪለትም፡፡
ከቦርድ አባላት ጋር ተነጋግሬ ይህን ጭቅጭቅና ጠብ ፈትተን በሠላማዊ መንገድ መስራት አለብን በሚል ብዙ ሥራዎች ተሠሩ፡፡ መጀመሪያ ኮሚቴ አቋቋምኩኝ፤የሚጣሉበትን ነገር አጣራን፤ኮሚቴው የውሳኔ ሃሳብ ሲያቀርብ የሚበጣበጡ ሰዎችን ኮሚቴ ውስጥ በመክተት ገለልተኛ የሆኑ ሰዎችንም ጨምሬ በሠላማዊ መንገድ ተነጋግረን ችግሩን ፈታን፡፡ አንድ ወር ተኩል ባልሞላ ጊዜ ነው ችግሩ የተፈታው፡፡
የህንፃውን ጉዳይ በተመለከተ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር በደብዳቤ ባሳወቁት መሠረት፤ “አዲስ አበባ ቻምበር በባለቤትነት ይዞት አዲስ አበባም ሆነ ሌሎች የክልል ቻምበሮች እንዲገለገሉበት፤የራሳቸውን ህንፃ እያሰሩ ሲወጡ ቀሪው ለኢትዮጵያ ቻምበር እንዲሆንና እያከራየ እንዲጠቀም እንዲሁም የክልል ቻምበሮችን እንዲያጠናክርበት ይሁን” በሚል ተስማምተን አሁን በፍቅርና በሠላም ብዙ ነገሮችን በጋራ እንሠራለን፡፡ አሁን እንደውም እኛ ስራ ሲበዛበን አዲስ አበባ ቻምበሮችን አግዙን እንላለን፤ እኛም እነሱን እናግዛለን፡፡ እንደ ዱሮው መገለማመጥና የጐሪጥ መተያየት ፈጽሞ ተወግዷል፡፡ በአመት ሁለት ጊዜ የመገናኛና የመሰብሰቢያ ፕሮግራም ሁሉ አዘጋጅተው እርስ በእርስ ይገባበዛሉ ይጨዋወታሉ፡፡
ከመንግስት ቢሮዎችና ከንግዱ ጋር ከተገናኙ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ጋር ያላችሁ የስራ ግንኙነት ምን ይመስላል?
ከ10 እና ከ15 ዓመት በፊት ሲለፋበት የኖረን ጉዳይ ነው፤ አሁን እኛ በተሳካ ሁኔታ እየሠራን ያለነው፡፡ ለምሣሌ ከንግድ ሚኒስቴር፣ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ከገቢዎችና ጉምሩክ፣ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ወዘተ ስንተዋወቅና አብረን መስራት እንፈልጋለን ስንል ሁሉም እውነት አልመሰላቸውም ነበር፡፡ ምክንያቱም ንግድ ምክር ቤት ከመንግስት ጋር አብሮ መስራት አይፈልግም የሚል እምነት ነበራቸው፡፡ እኛ ግን ከመንግስት ጋር የመስራት ጽኑ ፍላጐት አለን፡፡ ምክንያቱም ህግና ፖሊሲ የማያወጣው መንግስት ነው፡፡ ህግና ፖሊሲ ከሚያወጣ መንግስት ጋር አብሮ አለመስራት ደግሞ መልካም አይደለም በሚል ተነጋግረን፣ ከእነርሱ ጋር ሁለትና ሶስት የምክክር መድረኮች አካሂደናል፡፡ ይህን በብሔራዊም በክልልም ደረጃ አድርገነዋል፡፡ ከተመካከርንባቸው ውስጥ የወደብ ዕቃ ማንሳት ጉዳይ፣ ህዝቡ የተጯጯኸበት የንግድ ምዝገባ ጉዳይ፣ የታክስ አከፋፈልና የመሳሰሉት ላይ ተወያይተን አሁን ህጉን ሊያሻሽሉት ነው፡፡ ለምሣሌ ከጉምሩክ ጋር ባካሄድነው ውይይት ከመንግስት ጋር ይጣላሉ ተቀባይነት አያገኙም ሲሉን፣ መንግስት 98 በመቶውን የኛን ሃሳብ ተቀብሏል፡፡ ከላይ በጠቀስኩልሽ በታክስ አከፋፈል፣ በወደብ ዕቃ አነሳስ፣ በንግድ ምዝገባና በበርካታ ጉዳዮች ለንግዱ ማህበረሰብም ሆነ ለመንግስት ይጠቅማሉ ባልናቸው ሃሳቦች ላይ ነው መንግስት 98 በመቶ ሃሳባችንን የተቀበለው፡፡ “ያልተጠበቀ የመንግስት አቋም” ተብሎ ተወድሷል፡፡ በአጠቃላይ ያተኮርነው ለንግዱ ህብረተሰብ ምቹ የንግድ ከባቢን የመፍጠር ስራ ላይ ነው፡፡
አገሪቱ ውስጥ የተለያየ ፍላጐትና ባህሪ ያላቸው ነጋዴዎች አሉ፡፡ የንግዱን ማህበረሰብ የማስተዳደሩ ጉዳይ ምን ይመስላል?
እኛ የአገሪቱ የንግድ ማህበረሰብ ጥሩ ስነ - ምግባር ያለውና ታማኝ እንዲሆን የማንቃት፣ በተሳሳተ መንገድ የሚጓዙ ካሉ ወደ መስመር የመመለስ፣በሰዓቱ ግብር እንዲከፍሉና በንግድ ሥራ የሀገራቸውን መልካም ገጽታ እንዲገነቡ ጥረት እያደረግን ነው፡፡ እርግጥ ነው በርካታ ነጋዴዎች አሉ፣የተለያየ ባህሪ መኖሩም አይካድም፣ ነገር ግን በመልካም አቀራረብና አዎንታዊ መንፈስ በተሞላበት ሁኔታ ችግሮቻችንን እንፈታለን፡፡
የነጋዴውን ጥቅም በማስከበርና ከመንግስት ጋር ቅርርብ እንዲኖር የበኩላችንን እያደረግን ነው፡፡
አባላቱ በርካታ ቢሆኑም ነጋዴውን በመቅረብና በማነጋገር በቀላሉ ጤናማ በሆነ መንገድ መምራት ይችላል፡፡
በደርግ መንግስት ተወርሶ የነበረው ህንፃችሁ ተመልሶላችኋል፡፡ ሆኖም አዲስ ህንፃ ለማስገንባት ለአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ የቦታ ጥያቄ ማቅረባችሁን፣ምን ያህል ቦታና የት ቦታ እንደምትፈልጉ ከንቲባ ኩማ ደመቅሳ አሳውቁን ማለታቸውን ሰምቻለሁ፡፡ ያሁኑ ህንፃ እያለ ሌላ መገንባት የፈለጋችሁት ለምንድን ነው? ህንፃውን የምትገነቡበት ገንዘብ ከየት የሚገኝ ነው? ምን አይነት ህንፃስ ለማስገንባት አሠባችሁ?
ህንፃውን የማስመለስ ሥራ ረጅም ጊዜ ወስዷል፡፡ ከአስራ አምስትና አስራ ስድስት ዓመት በላይ ማለት ነው፡፡ ይሄ ህንፃ የተሠራው የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ሳይመሠረት በፊት ነው፤ አዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት በሚል የተሠራው፡፡ ስለዚህ አዲስ አበባ ቻምበር ይመለስልኝ ይላል፡፡ ኢትዮጵያ ቻምበርም ይመለስልኝ የሚል ደብዳቤ ሲያስገባ ቆይቷል፡፡ በኋላ ግን እኛ ምን አልን ---- የሚመለስ ከሆነ ለኢትዮጵያም ሆነ ለአዲስ አበባ ይመለስ የሚል አቋም ላይ ደረስን፡፡ በዚህ ሁኔታ መንግስት ህንፃውን ሲመልስ ኢትዮጵያ ቻምበር በባለቤትነት ይያዘውና መጠቀሙን አብረው ይጠቀሙ ሲል፤ አዲስ አበባ ደግሞ ኢትዮጵያ ቻምበር ሳይፈጠር የራሴ ነበር ይላል፡፡ ይሄው ይጠቀሙ ሲል አዲስ አበባ ደግሞ ኢትዮጵያ ቻምበር ሳይፈጠር የራሴ ነበር ይላል፡፡ ይሄ ጭቅጭቅ በነበረበት ወቅት እኛ በጭቅጭቅ ጊዜም ገንዘብም ከምናባክን ለአንዳችን ተመልሶ በጋራ ለምን አንጠቀምም፤ ከዚያስ ለምን የራሳችንን ህንፃ አንሰራም በሚል የአዲስ አበባው ንግድ ምክር ቤት ቦታ ጠይቆ ስራ ጀምሯል፡፡
እኛም ቦታ የጠየቅነው ለዚህ ነው፡፡ ህንፃው ከሁለት ዓመት በፊት ከተመለሰ በኋላ ግን ተከፋፍሎ በሠላም መጠቀም አልተቻለም፡፡ ስለዚህ እኛ ተመካክረን መንግስትን የወሰነውን ተግባራዊ ወደማድረግ ሄድን፡፡
ምክንያቱም መንግስት በዚህ በዚህ መልኩ ይጠቀሙ የሚል መመሪያ አስቀምጧል፡፡
አዲሱን ህንፃ ለመገንባት የታሰበበት ዋናው ምክንያት በየሀገሩ ሄደን የንግድ ምክር ቤት ቢሮዎችን ስንጐበኝ የምናያቸው ከእኛ ጋር ፈጽሞ አይገናኙም፡፡ የእኛ በጣም ያሳፍራል፡፡ የውጭዎቹ የአብዛኛዎቹ ቢሯቸው ህንፃው ራሱ ቤተ - መንግስት ነው የሚመስለው፤የእኛ ግን ከ60 እና 70 ዓመት በፊት የተሠራ ህንፃ ነው፡፡ እንደውም ያኔ ባለራዕይ ሆነው ይሄን ሰሩ እንጂ አሁን ያለበት ሁኔታ እንኳን ከአለም አቀፍ ንግድ ምክር ቤቶች ከክልል ምክር ቤቶች ጋርም መወዳደር አይችልም፡፡ በዚህ ምክንያት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባን ቦታ ጠይቀናል፡፡ አለምአቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የስብሰባ አዳራሽ፣ ቢሮዎች በአጠቃላይ የትኛውም አለምአቀፍ ሰው ቢመጣ አንገታችንን ቀና አድርገን የምናስገባበት መሆን መቻል አለበት፡፡ አሁን የአገራችን ኢኮኖሚ እያደገ ስለሆነ ብዙ ባለሀብቶች ኢትዮጵያ ውስጥ ኢንቨስት ለማድረግ እየመጡ ነው፡፡ ሲመጡ ደግሞ ንግድ ምክር ቤቱን ያነጋግራሉ፡፡ ያኔ የእኛ ቢሮ እንዲህ የሚያሳፍር ከሆነ ልክ አይመጣም፤ስለዚህ ቦታውን ሊሰጡን ፈቃደኛ ናቸው፡፡ ሁሉም ክልሎች ቦታ ተሰጥቷቸው ንግድ ምክር ቤት እንዲሠሩ እያልን ነው፡፡ የድሬዳዋው ንግድ ምክር ቤት ህንፃ እንዲመለስ ደብዳቤ መንግስት ጽፏል፤አፈፃፀም ነው የቀረው፡፡ በሌላ በኩል የንግዱ ማህበረሰብ ድምጽ እንዲሰማና ትኩረት እንዲያገኝ የአባላት ማብዛት ሥራ በከፍተኛ ሁኔታ ተሠርቷል፡፡ ለምሳሌ ትግራይ 16ሺህ ደርሷል፡፡ ደቡብም አማራም የአባላት ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ አድጓል፡፡ ጠንካራ ስራ ሠርቶ አባላትን በከፍተኛ ሁኔታ ላበዛ ክልል ሽልማት እንሸልማለን ብለን ሁሉም በፉክክር በጥሩ ሁኔታ እየሠራ ነው፡፡ አሁን የምንጠይቀው መሬት በከተማ ውስጥ ሆኖ ስፋቱም ምክንያታዊ የሆነ ነው፡፡
መጀመሪያ ለቢሮ ነው የምንጠይቀው፡፡ ከዚያ በኋላ አለም ዓቀፍ ኤግዚቢሽን የምናሳይበት ከከተማ ውጭ ቦታ መጠየቃችን አይቀርም፡፡
ቻምበር አካዳሚ ለማቋቋም ሀሳብ እንዳላችሁ ሰምቻለሁ፡፡ ምንድነው የሚሰራው? ዘርዘር ያለ ማብራሪያ ቢሰጡኝ----
ቻምበር አካዳሚ የሚለውን ስም አስጠንተናል ቻምበር አካዳሚ ከሚባል በቀላሉ “ሊደርሺፕ ኢንተርፕሪነርሺፕ ኤንድ ማኔጅመንት ሴንተር” እንዲባል ተስማምተናል፡፡ አመራርን፣ ስራ ፈጠራን እንደዚሁም ሥራ አመራርን አካትቶ ከተቋቋመ የላቁ ሰዎችን - መሪዎችን፣ የቦርድ አመራሮችን፣ የአገር መሪዎችን ወዘተ ከአፍሪካም ሆነ ከዓለም የሚያሰለጥን የልቀት ማዕከል ሊሆን ይችላል፡፡ ሥራ ፈጠራ ላይ በተለይ የሚያሰለጥን በቂ ተቋም የለም፡፡ ስለዚህ ሰዎች ችግር ከመፍራት ይልቅ መፍትሔ ፈጣሪ እንዲሆኑና የአስተሳሰብ ለውጥ እንዲያዳብሩ ማስተማር የሚችል ማዕከል ይሆናል፡፡ በማኔጅመንትም በኩል አገራችን ላይ ጉልህ የማኔጅመንት ችግር አለ፡፡ ስለዚህ ሰዎች በብቃት የመምራትና የማስተባበር ችግርን አስወግደው የላቀ ብቃት የሚያገኙበት ይሆናል፡፡ ይህንን ስንልም ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለዓለምም ነው፡፡ ለምሣሌ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ከውጭ ሁሉ መጥተው የሚሠለጥኑበት ሆኗል፡፡ ራዕይ ባላቸው ሰዎች ነው አየር መንገዱ ለዚህ የደረሰው፡፡ አሁን የእኛን ሃሳብ የሚያጣጥሉ አንዳንድ ሰዎች አሉ፤ ነገር ግን በእርግጠኝነት ዕውን እናደርገዋለን ብለን እናስባለን፡፡
በአሁን ሰዓት የመጀመሪያዋ ሴት የኢትዮጵያ የንግድ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ለመሆን በቅተዋል፤ የመጀመሪያዋ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትር የመሆን ሃሳብስ የለዎትም?
(ሣ…ቅ) እኔ ፖለቲከኛ አይደለሁም፡፡ ፖለቲከኞች ናቸው ለስልጣን ተነሳስተው የሚሄዱት፡፡ እኔ እዛ ወጥቼ ባልመራም በየትኛውም ቦታ ላይ መሪ ነኝ ብዬ አምናለሁ፡፡ ለምሣሌ እኔ ጥሩ ሃሳብ አምጥቼ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሥራ ላይ ካዋለው እኔ ነኝ የመራሁት ማለት ነው፡፡ ለምሣሌ አንቺ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኀይለማርያም ጥሩ ሃሳብ አቅርበሽ ሥራ ላይ ካዋሉት የመራሽው አንቺ ነሽ፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች የሚያዩት ወንበር ላይ መቀመጡን ነው፤ እኔ ግን የምፈልገው ስራ መሠራቱን ነው፡፡ አንቺ ከልብሽ ከሠራሽና ከተንቀሳቀሽ አንቺ ባትፈልጊም ስራው ይፈልግሻል፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትርነቱ ጥያቄ ገፍቶ ቢመጣስ አልፈልግም ትያለሽ?
አዎ እምቢ እላቸዋለሁ፡፡ ለምን መሠለሽ? እናንተ ምሩ፤ እኛ ከኋላ እናሠራለን እላቸዋለሁ፡፡ እኔ ፖለቲከኛ ስላልሆንኩ ነው፡፡ እዛ ቦታ ላይ መቀመጥ ያለባቸው ፖለቲከኞች ናቸው፡፡ አንድ ጋዜጠኛ ባለፈው ለምንድነው ፖለቲካ ውስጥ የማትሳተፊው ሲለኝ ነበር፡፡ እኔ ግን የፖለቲካውን ቼዝና ዳማ ጨዋታ አልችልበትም፡፡ እኔ ፊት ለፊት የምናገር ሰው በመሆኔ የፖለቲካውን ድራማ አልችልም ብዬ መልሼለታለሁ፡፡
ይሄ የብቃት ጉዳይ አይደለም፤ሞክሮ መውደቅም ይቻላል፡፡ ለአንድ ሰው ዋናው ነገር የተቀመጠበት ቦታ ሳይሆን በቀናነት ባለበት ቦታ መስራት መቻሉ ነው፡፡ ቀና ሰው ስለሆንሽ ችግር አይገጥምሽም ማለት አይደለም፡፡ ብዙ ችግርና እንቅፋት አለ፡፡ ያንን እንቅፋት ረግጠሽ አንቺ ወደ ላይ ከፍ ማለት ነው ያለብሽ፡፡
አንዳንዱ የአንዱን ትከሻ ረግጦ ራሱ ከፍ ማለት ይፈልጋል፡፡ እኛ እንኳን ባለንበት ቦታ ብዙ ጫና አለ፡፡
እኔ አሁን ስራውን የቀጠልኩት ለችግርና ለመከራ ስለማልበገር ነው፡፡ እንቅፋት እኮ ከኖርማሉ መሬት ከፍ ያለ ነው፤ስለዚህ እዛ እንቅፋት ላይ ስትቆሚ የባሰ ከፍ ትያለሽ፡፡ ለዚህም ነው እኔ ከመከራ በላይ ነኝ ብዬ የማምነው፡፡
የቤተሰብ ሃላፊነት አለ፣ የስራ ሃላፊነት አለ፣ አሁን ደግሞ ለፒኤችዲ እየተማርሽ ነው፡፡ ይህን ሁሉ ሃላፊነት በአንድ ላይ መወጣት አይከብድም? እንዴት እየተወጣሽው ነው?
ይሄ የጊዜ ጉዳይ ነው እንግዲህ፡፡ አንዳንዴ በቻምበሩ በኩል በሙያሽ ከምትሠሪው በተጨማሪ በርካታ ስራዎች ይመጣሉ፡፡ ሌላው ቀርቶ ዛሬ ነፃ ነኝ ብለሽ ስታስቢ ያላሰብሻቸው ሥራዎች በፀሐፊዋ በኩል ይቀርቡልሻል፡፡
አለም አቀፍ ስብሰባ መምራት፣ የተለያዩ ሪሴፕሽኖች ላይ መገኘት የመሳሰሉት ለምሣሌ በአንድ ምሽት ሶስት ሪሴፕሽን ላይ እንድትገኚ ይፈለጋል፡፡ እኔ አንዱ ጋ ሄጄ ሌላው ጋ አንድ የቦርድ አባል ስልክ፣ ለምን ፕሬዚዳንቷ አልመጣችም ይላሉ፡፡ ስለዚህ አንዱ ጋ ቶሎ ግንባሬን አስመትቼ ሌላው ጋ ደግሞ እሮጣለሁ፡፡ ቻሌንጁ ብዙ ነው ግን ቁርጠኛ ከሆንሽ የማይሰራ የለም፡፡
ብዙ ጊዜ በዕቅድ እንቀሳቀሳለሁ፣ነገር ግን እቅዴን የሚያበላሹ ነገሮች ይመጣሉ፣አቻችሎ መሄድ ነው፡፡ እቤት ውስጥ እኔ ከሌለሁ የቤት ሠራተኛ አበላሽታ የምትጠብቅሽ ነገር ይኖራል፣የቤቴን መበላሸት ግን ከአገር ጉዳይ አላስቀድምም፤ ወደ መንግስት ሥራ እሄዳለሁ፤የትምህርቱም ጉዳይ በዚህ መልኩ ነው የሚሄደው፡፡ እኔ በትምህርት ልምዱ ስላለኝ ክላስ ሳልከታተል የምሠራቸው ስራዎች አሉ፡፡
ቃለምልልሱን ከማጠናቀቃችን በፊት ስኬት ለእርስዎ ምን ማለት እንደሆነ ቢነግሩኝ----
ስኬት ማለት ሰው የፈለገውን መሆን መቻል ነው፡፡ አንድ ሰው ስኬት ብሎ የሚያስበው በ10 ደቂቃ 100 ሜትር መሮጥ ሆኖ በሳምንትም ሆነ በ10 ደቂቃ ከጨረሰ ስኬት ነው፤ ግን ያ የስኬቱ መጨረሻ ሊሆን አይገባም፡፡ ከዛ የተሻለ ስራ ለመስራት መነሳት አለበት፡፡ አንድ ሰው ግቡ ጋ ሲደርስ ስኬት ነው፡፡
ግን የስኬቱ መጨረሻ መሆን የለበትም ብዬ ነው የማምነው፡፡
እኔ ሁሌም ችግርን መከራን አሸንፋለሁ፡፡ ለሌላ ስኬት እዘጋጃለሁ፡፡ በአጠቃላይ ለእኔ ስኬት ቀጣይነት ያለውና መሆን የምትፈልጊውን መሆን ማለት ነው፡፡

Friday, January 18, 2013

አባባ ተስፋዬ(Ababa Tesfaye interview)

Ababa Tesfaye interview

ከአባባ ኮሚኩ እስከ አባባ ተስፋዬ
ባውዛ፡- አባባ ተስፋዬ በመጀመሪያ ለቃለ መጠየቃችን ፈቃደኛ በመሆንዎ በባዉዛ
ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል በጣም እያመስገንኩ ወደ ጭዉዉት ልግባና

የት አካባቢ ነበር የተወለዱት?
አባባ ተስፋዬ- የተወለድኩት ከዱ የሚባል ሀገር ነው ባሌ ውስጥ ነው የሚገኘው፡፡
ባውዛ፡- ወደ አዲስ አበባ እንዴት መጡ?
አባባ ተስፋዬ፡- አባቴ ነው ሊያስተምሩኝ ያመጡኝ በኋላም ቀበና አካባቢ በአንድ የፈረንሳይ /ህርት ቤት ውስጥ ገባሁ አሁን ኮከበጽባህ ይባላል፡፡ አባቴ አቶ መንበረ ወርቅ ለሚባሉ ሰው አደራ ሰጥተውኝ ሄዱ በኋላ ጣሊያን ወደ
ሀገራችን ገባ፡፡
ባውዛ፡- አባትዎም በወቅቱ ለትምህርት ንቃት ነበራቸው ማለት ነው?
አባባ ተስፋዬ፡- እኔም የሚገርመኝ ይሄ ነው አባቴ በዚያን ጊዜ ምን አሰበው ወደ አዲስ አበባ እንዳመጡኝ በእውነት ይገርመኛል፡፡ በዚያን ጊዜ ለትምህርት ምን ያህል ጥሩ አመለካከት እንዳላቸው አስካሁን ይገርመኛል፡፡
ባውዛ፡- ስንት ዓመት ይሆኖት ነበር ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ?
አባባ ተስፋዬ፡- 12 ዓመት ቢሆነኝ ነው፡፡ ነገር ግን ገና 7 ዓመቴ ፊደል ጨርሼ ዳዊት መድገም ጀምሬ ነበር ጎበዝ ነበርኩ ቀልድም እይዝ ነበር፡፡
ባውዛ፡- በዚህ የሆናል አባትዎ ወደ አዲስ አበባ ያመጡዎት?
አባባ ተስፋዬ፡- ይሆናል፡፡
ባውዛ፡- ከዚያ በኋላ ጣሊያን ገባ እርስዎስ ትምህርትዎን ቀጠሉ?
አባባ ተስፋዬ፡- የለም----የለም--- የጣሊያን ባሪያ ሆንኩ አለቀ፡፡ ታሪኩ ብዙ ስለሆነ ጽፈህ አትጨርሰውም፡፡ ለጣሊያን ባሪያ ብሆንም በኋላ ጣሊያኑን ፈንክቼ ወደ ሐረር
አመለጥኩ ሳቅ-----
ባውዛ፡- ታዲያ ወደ ቴአትሩ ዓለም እንዴት ተቀላቀሉ?
አባባ ተስፋዬ፡- ጣሊያኑን ፈንክቼ በባቡር ወደ ሀረር ከሄዱኩም በኋላ ጣሊያኖች ያሰሩት ራስ ሆቴል ገብቼ ስራ ጀመርኩ በኋላም ልዑል መኮንን ሆቴሉን ስለገዙት የሆቴሉ ኃላፊ ሆንኩ፡፡ እዛ ሆቴል እየሰራሁ ሳለሁ እንግሊዞች (ሱድ አፍሪካውያን) ወደ ሀገራቸው ሲሸኙ የሀገራቸውን ማርሽ አሰሙ፡፡ በኋላ የእኛ ሀገር ሕዝብ መዝሙር የሚያሰማ ባለመኖሩ ቆጨኝና በቃሌ የሀገራችንን ሕዝብ መዝሙር ዘመርኩ በዚህ ጊዜ
ጃንሆይ ‹‹ማነው?›› ብለው ጠየቁ የእነ ግራዝማች ጥግነህ፣ የእነቀኝ አዝማች ቤተሰብ
መሆኔ ተነገራቸውና ወደ አዲስ አበባ እንድመጣ አስደረጉ በነገራችን ላይ አባቴና የአባቴ
ቤተሰቦች ያለቁት ኦጋዴንና ባሌ ውስጥ ነው፡፡

ባውዛ፡- አባትዎ አሳሽ (አስገባሪ) ነበሩ ይባላል?
አባባ ተስፋዬ፡-አዎ አሳሽ ናቸው፡፡ በዚያን ጊዜ አሳሽ ማለት አልገብርም ያለውን
ቦታ ለራስ መኮንን ያስገብሩ ነበር፡፡ (የአፄ ኃይለሥላሴ) አባት እና ወደ ሐረርና ጨርጮ
አካባቢዎች ብዙ ዘመቻ አድርገዋል፡፡ ይሄን ብቻ ባወራህ 1 ሰዓትም አይበቃህም፡፡
ባውዛ፡- እንግዲህ የኢትዩጰያን ሕዝብ መዝሙር ዘመሩና አዲስ አበባ እንዲመጡ
ተደረገ ከዛስ ምን ሆነ?
አባባ ተስፋዬ፡- ተማሪ እያለሁ ጀምሬ የኢትዩጵያን ሕዝብ መዝሙር አውቅ ነበር
ጣሊያንም ከገባ በኋላ አሮጌ ፒያኖ አግቼ ተለማምጄአለሁ፡፡ በሆቴሉም ውስጥ ሙዚቃ
እሞክር ነበር፡፡ ከዛ 1937 . እንደ ኢትዩጵያ አቆጣጠር በሀገራችን ኪነጥበብን
ለማቋቋም አዋጅ ተነገረ፡፡ በኋላም ማዘጋጃ ቤት ተቋቁሞ ስለነበረ እዚያ ገባሁ፡፡ አስራ አንድ ወር ያለ ደመወዝ ሰራሁ፡፡ ደመወዝ
ያልጠየኩበት ምክንያት በንጉሱ ትዕዛዝ
መምጣቴን በማሰብ ነበር፡፡ መብልና
መጠለያ ግን ተመቻችቶልኝ ነበር፡፡
የሙዚቃ ትምህርቴን ከተማርኩ በኋላ
በዚያው ቴአትር ቤት አክተር ሆንኩ፡፡
ባውዛ፡- የሴት ገጸ ባህሪ ወክለው ይጫወቱ
ነበር፡፡ በዛን ጊዜ ደግሞ 18 ዓመት
ጎረምሳ ነበሩና እንዴት አድርገው ነው
የሴት ድምጽ ማውጣት የቻሉት?
አባባ ተስፋዬ፡- ቀላል ነው እንደሴት
መሆን አሁንም የሴት ድምጽ ማውጣት
እችላለሁ፡፡ ልበልልህ----ሳቅ-----የሴት
ድምጽ ብቻ ሳይሆን መንጎራደዱንም
እችልበታለሁ ላሳይህ----ሳቅ-----
ባውዛ፡- ከዛስ በቴአትሩ እንዴት ቀጠሉ?
አዲስ ተስፋዬ፡- ከዛማ 1944 . ወደ
ኮሪያ ሄድኩ ኮሪያም ሄጄ ‹‹ጠላቤቷን››
የተሰኘውን ቴአትር የሴት ገጸ ባህሪ
ተላብሼ በደንብ ሰራሁ፡፡ ቀሚስ ለብሼ
ብታየኝ ምኔም ወንድ አይመስልም ነበር
‹‹
ምናልሸኝ----!›› ያልኩ እንደሆን ሴትም
አስንቀ ነበር፡፡ በኋላም ብሔራዊ ቴአትር
1948 . ተከፈተ ድሮ መጀመሪያ
ማዘጋጃ ቤት የነበርን አክተሮች በሙሉ
ወደዚያ ተዛወርን የጃንሆይ ኢዩቤልዩ
በዓል ነበር፡፡ በደመቀ ስነ-ስርዓት ነበር
የተከፈተው ከዚያ በኋላ አክተር ሆኜ ስሰራ
ቆየሁ፡፡
ባውዛ፡- ከዛ በኋላ ወደ ኢትዩጵያ
ቴሌቭዥን እንዴት ገቡ?
አበባ ተስፋዬ፡- 1957 . በማዘጋጃ
ቤት ውስጥ የኢትዩጵያ ቴሌቭዥን
ሲመሰረት ነው የገባሁት በወቅቱ
የእንግሊዟ ንግስት ኤልሳቤት ትመጣለች
ተብሎ ነው።
ባውዛ፡- የቴሌቭዥን ዝግጅቱ
የተጧጧፈው ሙዚቃም ስናጠና ነበር፡፡
በኋላም 1957 ህዳር 1 ቀን የኢትዩጵያ
ቴሌቪዥን የልጆች ኘሮግራም ተጀመረ፡፡
ኘሮግራሙ የተጀመረው ደግሞ በእኔ
ጠያቂነት ነበር፡፡ በወቅቱ የቴሌቭዥን
ኃላፊ ሆነው ሲሰሩ የነበሩት ብላታ
ግርማቸው ተክለሀዋሪያት ነበሩ፡፡ በወቅቱ
ቴክኒሻኖቹ ፈረንጆች ነበሩ፡፡ ብላታ
ግርማቸው የሕፃናት ኘሮግራም አሰፈላጊ
መሆኑን ስነግራቸው ይሄም አለ እንዴ
‹‹
ብለው ፈረንጁን አማከሩት ፈረንጁም
‹‹
ሰው አላችሁ›› ብሎ ጠየቀ በኋላ እኔ
ተመርጬ ስቱዲዮ ገባሁ፡፡
ባውዛ፡- የልጆች ኘሮግራም እንደጀመሩ
ሲያቀርቡ የነበሩት የኘሮግራም ይዘት ምን
ነበር?
አባባ ተስፋዬ፡- ተረት ነበር
የማቀርበው፡፡
ባውዛ፡- ተረቱን ከየት ነበር የሚያገኙት?
አባባ ተስፋዬ፡- ድሮ በልጅነቴ አባቴና
አያቴ ብዙ ተረት ይነግሩኝ ነበር፡፡ እኔ
ደግሞ የማስታወስ ችሎታዬ ከድሮ ጀምሮ
ትልቅ ነበር፡፡
ባውዛ፡- መቼ መቼ ነበር ኘሮራሙን
የሚያቀርቡት?
አባባ ተስፋዬ፡- ቅዳሜ፣ እሁድና ሰኞ
ነበር፡፡
ባውዛ፡- 1957 የተወለደ ሕፃን ዛሬ
ትልቅ ሰው ነውና በዛን ጊዜ የነበሩ ልጆች
ለኘሮግራሙ ያላቸው አስተያየት ምን
ይመስል ነበር?
አባባ ተስፋዬ፡- ዛሬ ወደ ውጭ አሜሪካ
የጋበዙኝ ሁሉ በዛን ጊዜ ሕፃን ነበሩ፡፡ከዛ
ጊዜ በኋላ የተወለዱ ብዙ ናቸው በዛሬ ጊዜ
በጣም እየረዱኝ ያሉት እነሱ ናቸው፡፡
ገንዘብ ይሰጡኛል ስልክ እየደወሉም
ያጽናኑኛል ወደ ኢትዩጵያ በሄዱ ቁጥር
ተረቶቼን ይገዛሉ በብዙ ነገር ያስቡኛል፡፡ የእኔን ተረቶችና ምክር እንደውለታ
ቆጥረው ያስቡኛል፡፡ ወላጆቻቸውም
እንዲሁ ያከብሩኛል፡፡ ልጆቻችንን
ከአልባሌ ስፍራ እንዲርቁ በማድረግዎት
እናመሰግንዎታለን ይሉኛል፡፡
ባውዛ፡- ለምን ያህል ጊዜ ነው በኢትዩጰያ
ቴሌቪዥን የልጆች ኘሮግራም የቀረቡት?
አባባ ተስፋዬ 42 ዓመት ያህል
ነው እስከተወሰነ ጊዜ ድረስ የአክተርንት
ስራዬንም ደርቤ ነበር የምሰራው እና ለዚህ
ሁሉ ዓመት ልጆችን በተረት ስመክርና
ሳዝናና ቆይቼአለሁ፡፡
ባውዛ፡- መቼም በወጣትነትዎ ነው
ይሄንን ስራ የጀመሩትና ሲጀምሩም ‹‹አባባ
ተስፋዬ›› ነበር የሚባሉት ወይስ ሌላ ስም
ነበርዎት?
አባባ ተስፋዬ፡- በፊት ጭምብል (ማክስ)
አድርጌም እሰራ ነበር መጠሪያዬም ‹‹አባባ
ኮሚኩ ነበር›› የሚባለው በኋላ በራሴ ስም
እንዲሆን ተደረገ፡፡
ባውዛ፡- ህፃናትን ለማዝናናት ሳይንሳዊ
ትምህርት ቀስመዋል እንዴ?
አባባ ተስፋዬ፡- በፍጹም በተፈጥሮዬ
ነው ፊቴን የምቀያይረው ደግሞም መርሳት
የሌለብህ አክተርም ጭምር ነኝ፡፡ ልጅም
ለመምከር እንደዚያ ፊትን መቀያየርም
ያስፈልጋል፡፡ የምናገረው በስሜት
በእንቅስቃስና ድራማቲክ በሆነ ነገር
ካልደገፍኩት ልጆች ይሰለቻሉ፡፡ ስለዚህ
ፊቴን በመቀያየር ተረቴን አቀርባለሁ
እንጂ ማንም አላስተማረኝም እግዚአብሔር
ነው የሰጠኝ የአባቴ ምክር የአያቴ ተረት
ነው ለዚህ ያበቃኝ ተማሪም እያለሁ
መሸለል መፎከር እወድ ስለነበር የቁጣ
የደስታና የሐዘን የፊት ቅርጽ ማሳየት
እችላለሁ፡፡
ባውዛ፡- 42 ዓመታት ያህል ከሰሩበት
የኢትዩጵያ ቴሌቭን የልጆች ክፍለ ጊዜ
ኘሮግራም ለምን ለቀቁ?
አባባ ተስፋዬ፡- መቼም ከልጅ የዋለ
ልጅ ነው ይባል የለ አንዲት ልጅ ተረት
ስተርት ያንን ምክንያት አደረጉና ‹‹ከዛሬ
ጀምሮ ኮንትራታችን አልቋል አሉኝ›› እሺ
ብዬ ወጣሁ፡፡
ባውዛ፡- በቃ በዚህ ምክንያት ስራዎትን
ለቀቁ ማለት ነው?
አባባ ተስፋዬ፡- እኔ የማውቀው
ይህንን ነው፡፡ የቀረውን ደግሞ ‹‹ለምን
ኮንትራቱን አቋረጣችሁበት›› ብለህ
እነሱን ጠይቃቸው እኔ በበኩሌ ምንም
የማውቀው ነገር የለም በወቅቱ ልጅቷ
ተረት ስትናገር ጠይቄአታለሁ ‹‹አንድ
ጋና እና አንድ ፈረንጅ ነበሩ ስትል አንድ
ጋና ነው ያለችው የዩኒሴፍ ተረት ነበር፡፡
እነርሱ ምን እንደተሰማቸው አላውቅም
ብቻ ይሄ ተረት እንደተላለፈ የስንብት
ደብዳቤ ሰጡኝ ‹‹ከዛሬ ጀምሮ ኮንትራትዎ
አብቅቷል›› አሉኝ እሺ ብዬ እጅ ነስቼ
ወጣሁ፡፡
ባውዛ፡- እርስዎ ግን በስራው መቀጠል
ይፈልጉ ነበር?
አባባ ተስፋዬ፡- እንዴ እኔ የተፈጠርኩት
ለልጆች ነው በመጣሁ ጊዜ ሀገሩ በጋዜጣ
በስልክ ተጨናንቆ ነበር ምንም እንኳ
የስንብት ደብዳቤውን ሲሰጡኝ እጅ ነስቼ
ብቀበልም ህፃናቱ ለእኔ ካላቸው ፍቅርና
አክብሮት አንፃር ግን ሀዘን ይሰማኛል፡፡
ባውዛ፡- አሜሪካንን እንዴት ያይዋታል?
አባባ ተስፋዬ፡- አሜሪካ ሀያል ናት፡፡
የዓለም ንጉሥ ናት ሁሉ ነገር እጃ ላይ
ነው፡፡ እኔ ግን ሀያል ሀገር የምለው
ሀገሬን ነው፡፡ ኢትዩጵያን እወዳታለሁ፡፡
‹‹
ወፍ የሚጮኸው እንዳገሩ ነው›› ይባል
የለ ከዚህ ውጭ በልጅነታቸው እኔ
የመከርኳቸው በዚሁ በአሜሪካ ይገኛሉ፡፡
እነዚህ ሰዎች ዛሬ ታላላቅ ሰዎች ሆነዋል፡፡
ስለዚህ እኔም ከኢትዩጵያ መጥቼ
ከእነርሱ ጋር በመገናኘቴ ደስታዬ ወደር
የለውም፡፡ ወደ አሜሪካ ስመጣም ባዶ
እጄን አልመጣሁም፡፡ ከአራት መቶ በላይ
መጽሐፍት ይዤ ነው የመጣሁት፡፡ በሲዲ
የተዘጋጀ ተረት ይዤአለሁ፡፡ እና ጥሩ ጊዜ
እንደማሳልፍ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
ባውዛ፡- ኢትዩጵያውያን ህፃናትን
እየመከሩ ያሳደጉት አባባ ተስፋዬ እርሶ
ግን ልጆች አልዎት?
አባባ ተስፋዬ፡- አዎ አሉኝ፡፡ ሶስት
ልጆች ወልጄ ነበር፡፡ ሁለቱ ሞቱብኝ
አንዱ ግን አድጎ ልጅ ወልዶአል፡፡
እግዚአብሔር ይመሰገን ልጅ ከስሬ
አይጠፋም፡፡ አሁን አሥራ አንድ ቤተሰብ
አብረን እንኖራለን በዚህም ደስ ይለኛል፡፡
ባውዛ፡- በመጨሻ ምን የሚሉት ምን
የሚያስተላልፉት መልክት አልዎት?
አባባ ተስፋዬ፡- ወደዚህ ወደ አሜሪካ
በዚህ እድሜዬ በመምጣቴ ደስተኛ ነኝ
እኔን ለመርዳት ብዙ ሰዎች ሲጥሩ
አያለሁ፡፡ ለእነሱም የላቀና የከበረ ምስጋና
እንዳለኝ በዚህ አጋጣሚ ንገርልኝ፡፡
አብዛኛውን ጊዜዬን ህፃናትን እየመከርኩ
በማሳለፌ ከምንም ባልተናነሰ ደስተኛ
ነኝ፡፡ የሚወዱኝ ልጆች ብዙ ናቸው፡፡
ወላጆቻቸው ቢሆንም ለእኔ ትልቅ
አክብሮት አላቸው፡፡ ባለፈው ታምሜ
ከሞት ላዳኑኝ ምስጋና ይድረሳቸው፡፡
በዚህ በአሜካ ተወልደው ያደጉ ህፃናትም
ሀገራቸውን እንዲያውቁ እንዲወዱ እና
ስለሀገራቸው የሚቆረቆሩ እንዲሆኑ
እንደምፈልግ ንገረልኝ፡፡ ሁሉምንም
እወዳቸዋለሁ፡፡ በተለይ በዚህ በአሜሪካ
የሚኖሩ ወላጆች ለልጆቻው የኢትዩጵያን
ተረት እንዲያስተምሩ በዚህ አጋጣሚ
እጠይቃለሁ፡፡ የአገራቸውን አኢትዮጵያን
ቋንቋ፣ባህልና ታሪክ እንዲያውቁ ማስተማር
ይኖርባቸዋል። ለዚሕም ወላጆቻቸው
ትልቅ አላፊነት አለባቸው፡፡
ባውዛ፡- ለኢትዩጵያ ቴሌቭዥን የልጆች
ክፍለ ጊዜን እንደሚሰናበቱ ሁሉ እኛንም
አሰናብቱን?
አባባ ተስፋዬ፡- አዎ አስታወስከኝ፡፡
‹‹
ደህና ሁኑ ልጆች----የዛሬ አበባዎች የነገ
ፍሬዎች----ደህና ሁኑ ልጆች----ደህና ሁኑ››
ባውዛ፡- አመሰግናለሁ አባባ ተስፋዬ
መልካም የአሜሪካ ቆይታ ይሁንልዎ፡፡
አባባ ተስፋዬ- እግዚአብሔር ይስጥልኝ
አመሰግናለሁ፡፡